Gesamtlänge aller Episoden: 5 days 14 hours 15 minutes
ጀማል ከበደ ከሳውዲ አረቢያ ጅዳ እስርቤት ድምፅ ሁኑን ይላሉ። ጥቁር አሚን ከ ደሴ ለሁለት የዝግጅታችን ተከታታይ እና ተሳታፊዎች ግጥም ገጥመዋል። «ቅድማያ ለሰው ልጆች የመኖር ሕልውና» የሚሉት ደግሞ መቶ አለቃ ውቤ ታሪኩ ናቸው።
እንደ መስቀል እና ጥምቀት ያሉ በአደባባይ የሚከበሩ በዓላትን ለምን ፋሲል እንደሚወዱ በዛሬው ዝግጅታችን ገልፀውልናል። "ሐበሻ ተፈጥሮ ሰው ሆኖ ከመኖር ምነው ችግኝ ሆኜ አውሮፓ ብፈጠር" የሚሉት ደግሞ የደሴው ጥቁር አሚን ናቸው። መቶ አለቃ ውቤ ከሀረር የእሳቸው ጊዜ ትውልድ ምን ያህል ለባህር በር መጠበቅ ይጨነቅ እንደነበር ይዘረዝራሉ።
መልኬ ገባያዉ ከአሶሳ የፃፉት መልዕክት ርዕስ ሕልም እልም ይላሉ። ምን አልመው ይሆን? መቶ አለቃ ውቤ ከሀረር «በአገራችን ለደረሰው ሁለንታናዊ ቀውስ የኃይል አማራጭ ብቸኛው አማራጭ አይደለም» ይላሉ። አድማጮች የመልዕክት መቀበያ ስልክ ቁጥራችን +49-228-429-164995 ነው። ልትፅፉልን ከፈለጋችሁ አድራሻችን Deutsche Welle Amharic Service 53110 Bonn Germany ። የኢሜል አድራሻችን amharic@dw.com ነው። በፌስ ቡክ ሜሴንጀር ወይም በቴሌግራም ላይ @dwamharicbot ብላችሁ ልትፅፉልን ወይም የድምፅ መልዕክት ልትልኩልን ትችላላችሁ።